FDRE Ministry of Agriculture

Category News

አቶ ኤሊያስ አብዱረህማን የወተት ምርታማነትን አንዴት አሳደጉ?

በሐረሪ ክልል በድሬ ጠያራ ወረዳ የሱቁል ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አቶ ኤሊያስ አብዱረህማን ከአርሶአደርነት ስራቸው ጎን ለጎን በዘመናዊ የወተት ላሞች እርባታ ውጤታማ ናቸው፡፡ “ከልብ ካለቀሱ እንባ አይገድም” ነውና ነገሩ የስኬታቸው መነሻ ፍላጎትና ተነሳሽነት ነበር፡፡ በአንድ ወቅት ከወደ ባቢሌ አካባቢ ነጋዴዎች ሲመጡ…

ስርዓተ-ምግብ ተኮር ግብርና ለሁለንተናዊ ብልፅግና!

በግብርናው ዘርፍ ምርትና ምርታማነትን ከማሳደግ ባሻገር ስርዓተ-ምግብ ተኮር ግብርናን ዕውን በማድረግ የአመጋገብ ስርዓቱ የተስተካከለ እንዲሁም ጤናማና አምራች የሆነ ማህበረሰብ መፍጠር ጊዜ የማይሰጠው አንገብጋቢ ጉዳይ ነው፡፡ በዚህም ግብርና ሚኒስቴር ከሌሎች የልማት አጋር አካላት ጋር በመተባበር እና በመቀናጀት ስርዓተ-ምግብ ተኮር ግብርናን ዕውን…

አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን ለአርሶአደሮች በማላመድ ላይ እየሰራ የሚገኘው ጆይቴክ ፋርም

በሀገራችን በግብርናው ዘርፍ የልማት መስክ ላይ የተሰማሩ ኩባንያዎች ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም የተለያዩ ምርቶችን ለሃገር ውስጥና ለውጭ ገበያ እያቀረቡ ይገኛሉ። ለአብነትም ጆይቴክ ፋርም በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች ዘመኑን የዋጁ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ዘርፉን የሚያዘምኑ የተለያዩ የልማት ስራዎችን በማከናወን ዘመናዊ ግብርናን ዕውን እያደረገ ይገኛል።…

የግብርና ምርት ውል (የኮንትራት እርሻ) የአምራቾችን የፋይናንስ ክፍተት እየሞላ ነው፡፡

/አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 10 ቀን 2018 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር/ ዘርፈ ብዙ ጠቀሜታ ያለው የግብርና ምርት ውል (የኮንትራት እርሻ)  በተጨባጭ ውጤት እያመጣ ሲሆን የግብርና ምርትን በመጠን፣ በጥራትና በአመራረት ቅልጥፍና ተወዳዳሪ ከማድረግ ባሻገር  የግብርና እና የአግሮ-ኢንዱስትሪ ተመጋጋቢነትን እያሳደገ ይገኛል፡፡ የኮንትራት እርሻ አስመራቾች…

የገጠር ልማታዊ ሴፍቲኔት ፕሮግራም የምግብ  ዋስትናውን ያረጋገጠ ሕብረተሰብ  ለመፍጠር በትኩረት  እየሰራ ነው፡፡

ስር የሰደደ  የምግብ ዋስትና ችግርን በቤተሰብና በሃገር ደረጃ  በዘላቂነት  ለመፍታት ድጋፍ የሚሹ የህብረተሰብ ክፍሎችን በመለየት በምግብ እራሳቸውን  እንዲችሉ ለማድረግ የገጠር ልማታዊ ሴፍትኔት ከሚተገበርባቸው ክልሎች የትግራይ ክልል አንዱ ነው፡፡ በትግራይ ክልል ታህታይ ማጨው ወረዳ  ናይ አጽሚ ቀበሌ እና በአድዋ ወረዳ ማሪያም…

የስንዴ ራስ አድርቅ በሽታ ምንድን ነው?

የስንዴ ራስ አድርቅ (Fusarium Head Blight) በመባል የሚታወቀው በሽታ በአለም ዙሪያ በስንዴና በሌሎች የብርዕ ሰብሎች ላይ ከፍተኛ የምርት ቅነሳና የጥራት ችግር የሚያመጣ የፈንገስ በሽታ ነው። ይህ በሽታ ስንዴን በዋናነት ከሚያጠቁ ፈንገሶች ውስጥ አንዱ ሲሆን ከ17 በላይ በሚደርሱ የተለያዩ የፉዛሪየም ዝርያዎች…

የግብርና ኢንቨስትመንት ምርትና ምርታማነትን እንንዲሁም የውጭ ምንዛሪን በማሳደግ ለሀገራዊ ዕድገት የላቀ አስተዋጽኦ እያበረከተ ነው

(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 27 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የግብርና ኢንቨስትመንት የሥራ ዕድልን በመፍጠርና የውጭ ምንዛሬን በማሳደግ  ለማክሮ ኢኮኖሚው ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ   ይገኛል።  በግብርና ኢንቨስትመንት  2.5 ሚሊዮን ሄ/ር መሬት እያለማ ነው። በግብርና ሚኒስቴር የግብርና ኢንቨስትመንትና ምርት ግብይት መሪ ሥራ አስፈጻሚ…

የእንስሳት ህክምና አገልግሎቱን ማዘመን ለእንስሳት ምርትና ምርታማነት ዕድገት ጉልህ ድርሻ ያበረክታል

(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 9 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) በኢትዮጵያ የእንስሳት ልማቱን ምርታማነት ለማሳደግ የእንስሳት በሽታን መከላከልና በዘላቂነት መቆጣጠር ላይ ሰፊ ተግባራቶች እየተከናወኑ ይገኛሉ፡፡ የዓለም አቀፉ የእንስሳት ጤና ድርጅት (WOAH) የእንስሳት ህክምና አገልግሎት አፈጻጸም(PVS) የክትትልና ግምገማ ባለሙያዎች ቡድን በኢትዮጵያ ያለውን…

በግብርናው ዘርፍ የፋይናንስና ኢንሹራንስ ተደራሽነትን ለማስፋት እየተሰራ ነው

(አዲስ አበባ፣ ሰኔ 4 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) ግብርና ሚኒስቴር ዘርፉን ከሚደግፉ አጋር አካላት ጋር በመሆን ለአየር ንብረት ለውጥ ተጋላጭ የሆኑና በአነስተኛ ማሳ የሚያመርቱ አርሶና አርብቶ አደሮችን የፋይናንስ አቅም ለማሳደግ በትኩረት እየሰራ ይገኛል። በዚህም የገጠር ፋይናንስ ዩኒት በማቋቋም ሚኒስቴር…

ለንቦች ምቹ ስነ-ምህዳር በመፍጠር ምርትና ምርታማነትን ማሳደግ ይገባል

(ጅማ፣ ግንቦት 12 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) ዓለም አቀፍ የንብ ቀን እና 2ኛው ዘላቂ የንብ ማነብና እጽዋት ተራክቦ ጉባኤ በጅማ ከተማ የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች እንዲሁም ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት እየተካሄደ ይገኛል፡፡ ኢትዮጵያ ከተባበሩት መንግስታት የምግብና የእርሻ…

ግብርናው ከምግብ ዋስትና ማረጋገጥ ባለፈ ለወጪ ንግድ ግኝት ያለው አስተዋፅኦ በእጅጉ ጨምሯል፡- ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

/አዳማ፣ ሚያዝያ 25፣ 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር/ ባለፉት ዘጠኝ ወራት በሁሉም የግብርና ዘርፎች የተገኙ ውጤቶች ግብርናው በኢኮኖሚ ዘርፉ ያለውን የመሪነት ሚና የሚያሳይና የሚያረጋግጥ ነው፡፡ የግብርና ሚኒስቴር፣ ተጠሪ ተቋማትና ክልሎች በዘርፉ የ9 ወር እቅድ አፈጻጸም ስኬቶችና በታዩ ክፍተቶች ላይ ያተኮረ ውይይት…

ምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም የግብርናውን ዘርፍ ምርታማነት ከማሳደግ አኳያ የራሱን አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል

(ሐዋሳ፣ ሚያዝያ 21 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) በግብርና ሚኒስቴር የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ተግባራዊ መደረግ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ባለፉት ሁለት አመታት ውስጥ የዘርፉን ምርትና ምርታማነት ከማሳደግ በተጨማሪ የስራ ዕድል በመፍጠርም የራሱን አስተዋፅዖ እያበረከተ ይገኛል፡፡ የምግብ ስርዓት ማጠናከሪያ ፕሮግራም ከክልሎች…

የመሬት ይዞታ ማረጋገጫ ሰርተፊኬት የአርሶአደሩን ዘርፈ-ብዙ ተጠቃሚነት የሚያረጋግጥ ነው

/ይርጋ ጨፌ፣ ሚያዝያ 19 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር/ የግብርናውን ምርትና ምርታማነት በማሳደግ ሂደት ውስጥ የተሳለጠ የገጠር መሬት አስተዳደር መረጃ ስርዓትን ማዘመንና መተግበር ይገባል፡፡ ይህ ደግሞ አርሶአደሩን የመሬት ይዞታ ባለቤትነቱን በማረጋገጥ ምርታማና ተጠቃሚ እንዲሆን ያስችለዋል፡፡ ግብርና ሚኒስቴር የአርሶአደሩን የመሬት ይዞታ…

የግብርናውን ትራንስፎርሜሽን እውን ለማድረግ በዘርፉ ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች ድርሻ የጎላ ነው፡- የተከበሩ አቶ ሰለሞን ላሌ

 /ሀዋሳ፣ ሚያዝያ 17፣ 2017ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር/ ግብርና እንደ ሀገር መዋቅራዊ ሽግግሩን እውን ለማድረግ በሚያደርገው ጉዞ   የግብርናው ኢንቨስትመንት ጉልህ ሚና አለው፡፡ በሲዳማ ክልል በግብርና ኢንቨስትመንት ላይ የተሰማሩ ባለሃብቶች አፈጻፀም፣ በዘርፉ የሴቶች ተሳትፎና ሚና፣ በዘርፉ ያሉ መልካም እድሎች፣  በክልሉ ኢንቨስትመንትን ለማስፋፋት ያሉ…

ባለፉት 5 አመታት ለተመዘገበው ተከታታይ ሀገራዊ እድገት ግብርናው የመሪነት ሚናውን ተወጥቷል፡- ክብርት አይናለም ንጉሴ

/አዲስ አበባ፣ ሚያዝያ 8 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር/ ሀገራዊ ለውጡ እውን ከሆነ በኋላ ባለፉት ተከታታይ አመታት የማክሮ ኢኮኖሚ እድገቱ አመርቂ ውጤት የተመዘገበበት ሲሆን የግብርናው ዘርፍ ለእድገቱ የራሱን ትልቅ ድርሻ እየተወጣ ይገኛል፡፡ የግብርና ሚኒስቴር እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ባለሙያዎች የ2017…

ግብርናው የአርሶ/አርብቶ አደሩን የእውቀት እና የቴክኖሎጂ ፍላጐት የሚመጥን የኤክስቴንሽን አገልግሎት መስጠት ይገባል፡- ግርማ አመንቴ(ዶ/ር)

/ኮምቦልቻ፣ መጋቢት 29 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር/ የግብርና ኤክስቴንሽን ስርዓት ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ፣ የምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ እንዲሁም ገበያ ተኮር ምርቶችን በማምረት የሀገራችንን ኢኮኖሚ ወደ ተሻለ ደረጃ ለማድረስ ወሳኝ ተግባር ነው፡፡ በመሆኑም አዳዲስ የግብርና ቴክኖሎጂዎችን እና የተሻሻሉ አሰራሮችን…

በአፋር ክልል ከጊዜ ወደ ጊዜ እያደገ የመጣውን የሰብል ምርታማነት ይበልጥ ለማሳደግ በቅንጅት እየተሰራ ነው

(ሰመራ፣ መጋቢት 25 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) እንደ ሃገር ባለፉት ስድስት ተከታታይ ዓመታት የስንዴ ምርትን በከፍተኛ ደረጃ በማሳደግ ከሃገር ውስጥ ፍጆታ አልፎ ወደ ውጭ ኤክስፖርት ለማድረግ በተደረጉ እንቅስቃሴዎች አበረታች ውጤቶች ተመዝግበዋል። እነዚህንም አበረታች ውጤቶች ቀጣይነታቸውን ለማረጋገጥ እና ለማስፋፋት ግብርና…

የግብርናውን ምርታማነት ከማሳደግ ባለፈ ጥራትና ደህንነቱን የጠበቀ ስርዓተ ምግብ ተኮር ግብርና ማድረግ ያስፈልጋል

/ባህርዳር፣ መጋቢት 25፣ 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር/ ለአንድ ሀገር ሁለንተናዊ ብልፅግና  አካላዊ እና አዕምሯዊ እድገቱ የተረጋገጠ እና ምርታማ የሆነ ትውልድ መፍጠር ወሳኝ ሚና አለው፡፡ የግብርና ሚኒስቴር የግብርና ምርትና ምርታማነት በመጨመርና በምግብ ራስን ለመቻል ከሚደረገው ጎን ለጎን የምግብና ስርዓተ ምግብ ዋስትና…

የተፋሰስ ልማት በአማራ ክልል

(አዲስ አበባ፣ መጋቢት 22 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) አማራ ክልል የዓባይ፣ የአዋሽ፣ የተከዜ እና የደናኪል ተፋሰሶች መገኛ ነው። ከአጠቃላይ የዓባይ ተፋሰስ ደግሞ 60 በመቶ የሚኾነውን የሚሸፍነው የአማራ ክልል ነው። እንደ አሚኮ ዘገባ፤ ምሥራቅ ጎጃም፣ ምዕራብ ጎጃም፣ ሰሜን ጎጃም፣ አዊ…

የተቀናጀ የተፋሰስ ልማት በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ  ክልል  በርካታ ውጤቶችን አስገኝቷል

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ  ክልል  በተቀናጀ የተፋሰስ ልማት  በርካታ ውጤቶችን ማስመዝገብ ተችሏል፡፡ ባለፉት ቅርብ አመታት የተሰሩት የአፈርና ውሃ ጥበቃና የአርንጓዴ አሻራ  የችግኝ ተከላ ፕሮግራሞችን በማካሄድ የተራቆቱ አከባቢዎች አገግመዋል፤ ምርትና ምርታማነትም ጨምሯል፤ የደረቁ ምንጮች  በቂ ውሃ ማፈለቅ ጀምረዋል እንዲሁም አርሶ አደሮች የመኖ…

የለውጡ ፍሬዎች በእንስሳት ሃብት ልማት ዘርፍ

የእንስሳት እና ዓሳ ሀብት ልማት ዘርፍ በፊት የተሰጠው ትኩረት አናሳ በመሆኑ ምክኒያት ሀገራችን ባላት የእንስሳት ቁጥር ልክ ሳንጠቀም ቄይተናል፡፡ ባለፉት 7 የለውጥ ዓመታት ግን ለእንስሳት ዘርፍ በተሰጠው ትኩረት በተለይም ሀገራዊ የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም በይፋ ከተጀመረ ወዲህ በዘርፉ ተጨባጭ ውጤቶችን ማስመዝገብ…

የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት ዘርፍ ፕሮጀክት የሌማት ትሩፋት ፕሮግራምን ከግብ ለማድረስ በርካታ ተግባራትን እያከናወነ ነው

(ወልቂጤ፣ መጋቢት 3 ቀን 2017 ዓ.ም፣ ግብርና ሚኒስቴር) የሌማት ትሩፋት ፕሮግራም በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) አነሳሽነት በ2014 ዓ.ም ተግባራዊ ከተደረገበት ዕለት ጀምሮ ለእንስሳትና ዓሳ ሃብት ዘርፉም መነቃቃትን ፈጥሯል። ይህንንም ሃገራዊ ኢኒሼቲቭ ከግብ ለማድረስ በግብርና ሚኒስቴር የእንስሳትና ዓሳ ሃብት ልማት…